ኢትዮጵያ እና እምነቷ በቅድመ ክርስትና ምዕራፍ ሁለት - አትሮንስ ዘተዋሕዶ

አትሮንስ ዘተዋሕዶ

በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ሥርዓትና ደንብን የጠበቁ ጽሑፎችና ምስሎች በመ/ር ቀሲስ ንጋቱ አበበ እየተዘጋጀ የሚቀርብበት ድኅረ ገጽ ነው።

Breaking

Post Top Ad

Responsive Ads Here

Saturday, October 12, 2019

ኢትዮጵያ እና እምነቷ በቅድመ ክርስትና ምዕራፍ ሁለት


ምዕራፍ ሁለት
2. ኢትዮጵያ እና እምነቷ በቅድመ ክርስ

2.1. የዛሬዋ ኢትዮጵያ በጥንቱ ዘመን አጠራር
. ኢትዮጵያ በጥንት ግብጻውያን አጠራር
Ø  የጥንት ግብጻውያን በአፍሪካ የስልጣኔ ፈር ቀዳጅ ሕዝቦች ናቸው፡፡
Ø  ለሥልጣኔያቸው የዓባይን ወንዝ መሰረት የደረጉት እነዚህ ሕዝቦች ፈርዖኖች በመባል በሚታወቁ ገዠዎቻቸው፣በፒራሚዶቻቸውና ሄሮግላፊክስ በሚባለው የአጻጻፍ ስልታቸው በዓለማችን የጥንት ታሪክ በሚገባ ይታወቃሉ፡፡
Ø የጥንቶቹ ግብጻውያን ‹‹ኢትዮጵያ››የሚለውን ስያሜ ከማግኘቷ በፊት በተለያየ መጠሪያ ያውቋት እንደነበር ይታመናል፡፡እነዚህም የሚከተሉት ናቸው፡፡
Ø .. ጱንጥ፤- ይህን ስያሜ አስመልክቶ ሁለት አይነት አስተያየቶች አሉ፡፡የመጀመሪያው ጱንጥ የተባለው ስም ከአራቱ የካም ልጆች አንዱ ከሆነው ‹‹ፉጥ›.ጋር ይመሰሰላል የሚለው ነው፡፡
Ø የካም ወንዶች ልጆች ስም ተጠቅሷል፡፡ እነዚህም  ሚዝራይም፣ኩሽ፣ ከነዓን እና ፉጥ ናቸው፡፡
Ø ዘፍ 16 እዚህ ላይ ኢትዮጵያን ያቀኗት የካም ልጆች /ዘሮች /ናቸው፡፡ የሚለው ትውፊታዊ ምስክርነት ስላለ ምን አልባትም በዚሁ ምንያት አገሪቱ ጱንጥ የሚለውን ስያሜ ከካም ልጆች  አንዱ በሆነው ፉጥ በሚለው አግኝታ ሊሆን ይችላል የሚል ነው ፡፡
Ø በሌላ አነጋገር የጥንት ግብጻውያን የታሪክ መረጃዎች በአፍሪካ ቀንድ ‹‹ፑንት››የሚባል ጥንታዊ መንግስት ትክክለኛው የግዛት ወሰን የታወቀ ባይሆንም የዛሬዋ ኢትዮጵያ በኢያ ስር እንደምትጠቃለል መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡
Ø በጥንታውያኑ ግብጾች አጻጻፍ በፒራሚዶች ላይ መረጃዎችም ግብጻውያን ፈርዖኖች ውድና ብርቅ የሆኑ ዕቃዎችን ‹‹ፑንት››ያገኙ እንደነበር ያመለክታሉ ፡፡
Ø በተለይም ዕጣን፣ የዝሆን ጥርስ፣ ወርቅ፣ ከርቤና የዐይን ኩል ዋና ዋነዎቹ ናቸው፡፡እነዚህ ነገሮችም በተለይ ከሌሎች በተሸለ የሚገኙት ኢትዮጵያ ክልል ውስጥ ነው፡፡
v ከሚታወቁት ታሪካዊ ማስረጃዎች ሌላ በሁለቱም አገሮች በጋራ የሚታወቁት አንዳንድ ቁሶች ይህንንሃሳብ ሚየጠናክሩ ናቸው፡፡ ለምሳሌ የሚከተሉትን እንውሰድ
ü የኢትዮጵያና የግብጽቆነጀጅቶችየሚጠቀሙበት የዐይን ቅባት በሁለቱም አገር ሰዎች እስከዛሬ ድረስ በተመሳሳይ መጠሪያ ‹‹ኩል›› በመባል ይታወቃል
ü በአገራችን የምንጠቀማቸው አንዳንድ ጌጣጌጦች /ለምሳሌ አምባር፣ጨሌ‹‹‹ የግብጻውያን ተፅዕኖ አለባቸው፡፡
ü ለቤተክርስቲያን አገልግሎት የሚውለው ዕጣን ጥንታውያን ግብጾች ለአምልኮአቸው ይጠቀሙበት እንደነበር የሚታወቅ ሲሆን አሁንም በሁለቱ አካባቢዎች በተመሳሳይ መጠሪያ ዕጣን ተብሎ ይታወቃል፡፤
ü ጸናጽል፣ዋሽንትየመሳሰሉት የመዝሙር መሳሪያዎች ጥንት መሰረታቸው ግብጽ እንደነበረ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡
ü አሁን በዝዋይና በጣና ሐይቆች አካባቢ የሚያገለግሉ ጀልባዎች ከጥንት ግብጻውያን ጀልባዎች ጋር በጣም ይመሳሰላሉ፡፡
ü እንግዲህ ይህ ሁሉ በአጋጣሚ የሆነ ነው ለማለት ያዳግታል፡፡
ü ይልቅስ ሁለቱ አገሮች በጥንታዊ ታሪክ የባህልና  የንግድ ግንኙነት እንደነበራቸው የሚጠቁምና ‹‹ጱንጥ››የሚለው ስያሜያቸው የሚያመለክተው በበርካታ ነገር የሚያውቁት የሚያውቁት የዛሬዋ ኢትዮጵያ እንደሆነ ያስረዳል፡፡
ü . -ኔቶር፤- ይህ ስያሜ የጥንት ግብጻውያን ለኢትዮጵያ ምድር የሰጡት ስያሜ እንደነበር ሲታወቅ ትርጉሙም ‹‹የአምላክ ሀገር›› ማለት ነው፡፡
ü ግብጻውያን የዛሬዋን ኢትዮጵያ አካባቢ ‹‹የአምላክ ሀገር ››ብለው መጥራታቸው ሁለት ዓበይት ምክንያቶች ሊሆን እንደሚችል ይታመናል፡፡
ü የመጀመሪያው ለግብጻውያን የሥልጣኔ መስረትና የኑሮ ዋስትና የሆነው የናይል (ዓባይ) ወንዝ መነሻ ስለሆነች ሲሆን
ü ሁለተኛው ደግሞ ጥንታውያን ግብጻውያን ለአማልክቶቻቸው የሚያቀርቡት ዕጣንና ሌሎች ውድ የሆኑ ሽቶዎች  የሚያገኑት ኢትዮጵያ ስለነበር ነው፡፡
ü .የኩሽ ምድር፤- ይህ ስያሜ ግብጾች ከሃገራቸው በስተደቡብ ያለውን ሰፊ ቦታ የሚያውቁበት ሌላኛው መጠሪያ ነው፡፡
ü ሊቀ ነቢያት ሙሴም ብሉይ ኪዳንን ሲጽፍ ኢትዮጵያን የኩሽ ምድር እያለ መጥራቱ በግብጽ ምድር ተወልዶ ማደጉንና የግብጻውያንን ባህልና ቋንቋ ያውቅ ስለነበር ነው፡፡
ü የመጽሐፍ ቅዱስ ሊቃውንት ደግሞ ኢትዮጵያ የኩሽ ምድር ተብላ  ስትጠራ የነበረችበት ምክንያት የካም የመጀመሪያ ልጅ የኩሽ ዘሮች ስለሰፈሩባት እንደሆን ይገልጻሉ፡፡ዘፍ 16 ፡፡

ü ከጌታ ልደት በፊት 284 ዓመት ብሉይ ኪዳንን ከዕብራይስጥ ወደ ግሪክኛ (ጽርዕ) የተረጎሙት ሰባው ሊቃውንትም ሙሴ ‹‹ኩሽ››እያለ የጻፈውን ‹‹ኢትዮጵያ›› በሚል የተኩትም በዚህ ምክንያት ነው፡፡

ይቀጥላል……………… 

Post Bottom Ad