✞✞✞ እንኩዋን ለቅዱሳን ሰማዕታት "ባኮስ ወሰርጊስ" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞✞✞
+"+ ቅዱሳን ባኮስ ወሰርጊስ +"+
=>ሰማዕትነት በክርስትና ለሃይማኖት የሚከፈል
የመጨረሻው ዋጋ (መስዋዕትነት) ነው:: ሰው ለፈጣሪው
ሰውነቱን ሊያስገዛ: ሃብት ንብረቱን ሊሰጥ ይችላል::
ከስጦታ በላይ ታላቅ ስጦታ ግን ራስን አሳልፎ መስጠት ነው::
የመጨረሻው ዋጋ (መስዋዕትነት) ነው:: ሰው ለፈጣሪው
ሰውነቱን ሊያስገዛ: ሃብት ንብረቱን ሊሰጥ ይችላል::
ከስጦታ በላይ ታላቅ ስጦታ ግን ራስን አሳልፎ መስጠት ነው::
+ራስን መስጠት በትዳርም ሆነ በምናኔ ውስጥ ይቻላል::
የመጨረሻ ደረጃው ግን ሰማዕትነት ነው:: "አማን መነኑ
ሰማዕት ጣዕማ ለዝ ዓለም: ወተዓገሡ ሞተ መሪረ
በእንተ መንግስተ ሰማያት" እንዳለው ቅዱስ ኤፍሬም
ሶርያዊ ሰማዕትነት ማለት መራራውን ሞት ስለ ፍቅረ
እግዚአብሔር ሲሉ መታገስ ነው::
የመጨረሻ ደረጃው ግን ሰማዕትነት ነው:: "አማን መነኑ
ሰማዕት ጣዕማ ለዝ ዓለም: ወተዓገሡ ሞተ መሪረ
በእንተ መንግስተ ሰማያት" እንዳለው ቅዱስ ኤፍሬም
ሶርያዊ ሰማዕትነት ማለት መራራውን ሞት ስለ ፍቅረ
እግዚአብሔር ሲሉ መታገስ ነው::
+እርሱ ቅሉ መድኃኒታችን ክርስቶስ የሰማይና የምድር
ጌታ ሲሆን ኃፍረተ መስቀልን ታግሦ ሙቶልን የለ!
በዓለም ያሉ ብዙ እምነቶች ስለ መግደል በቀጥታም ሆነ
በተዘዋዋሪ ያስተምራሉ:: ክርስትና ግን መሞትን እንጂ
መግደልን የሚመለከት ሕግ የለውም::
ጌታ ሲሆን ኃፍረተ መስቀልን ታግሦ ሙቶልን የለ!
በዓለም ያሉ ብዙ እምነቶች ስለ መግደል በቀጥታም ሆነ
በተዘዋዋሪ ያስተምራሉ:: ክርስትና ግን መሞትን እንጂ
መግደልን የሚመለከት ሕግ የለውም::
+እርሱ ባለቤቱ "ጠላቶቻችሁን ውደዱ: የሚረግሟችሁን
መርቁ: ስለሚያሳድዷችሁ ጸልዩ" ብሎናልና:: (ማቴ.
5:44) ነገር ግን ዕለት ዕለት ራሳችንን በሃይማኖትና
በምግባር ካልኮተኮትነው ክርስትና በአንድ ጀምበር
ፍጹም የሚኮንበት እምነት አይደለምና በፈተና መውደቅ
ይመጣል::
መርቁ: ስለሚያሳድዷችሁ ጸልዩ" ብሎናልና:: (ማቴ.
5:44) ነገር ግን ዕለት ዕለት ራሳችንን በሃይማኖትና
በምግባር ካልኮተኮትነው ክርስትና በአንድ ጀምበር
ፍጹም የሚኮንበት እምነት አይደለምና በፈተና መውደቅ
ይመጣል::
+በተለይ የዘመኑ ክርስቲያን ወጣቶች ልናስተውል
ይገባናል:: የቀደሙ ወጣት ሰማዕታት ዜና የሚነገረን
እንድንጸና ነውና::
ይገባናል:: የቀደሙ ወጣት ሰማዕታት ዜና የሚነገረን
እንድንጸና ነውና::
¤እስኪ ለዛሬ ደግሞ በአጭሩ የቅዱሳን ባኮስና ሰርጊስን
ዜና እንካፈል::
ዜና እንካፈል::
+እነዚህ ቅዱሳን የዘመነ ሰማዕታት ፍሬዎች ናቸው::
ባኮስ እና ሰርጊስ (ሰርግዮስ) ከልጅነት ጀምሮ ባልንጀሮች
ናቸው:: በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን በሮም ግዛት ሥር
መክስምያኖስና ዲዮቅልጢያኖስ እስከ ነገሡበት ዘመን ድረስ በአንጻሩም ቢሆን ሰላም
ነበር::
ባኮስ እና ሰርጊስ (ሰርግዮስ) ከልጅነት ጀምሮ ባልንጀሮች
ናቸው:: በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን በሮም ግዛት ሥር
መክስምያኖስና ዲዮቅልጢያኖስ እስከ ነገሡበት ዘመን ድረስ በአንጻሩም ቢሆን ሰላም
ነበር::
+ታዲያ በዚህ የሰላም ጊዜ 2ቱ ቅዱሳን ሥራ
አልፈቱም:: ጾምን: ጸሎትንና በጐ ምግባራትን ሁሉ
ይከተሉ ነበር:: ለመከራ ዘመን ስንቅ የሚሆነን በሰላሙ
ዘመን የተያዘ ስንቅ ነውና::
አልፈቱም:: ጾምን: ጸሎትንና በጐ ምግባራትን ሁሉ
ይከተሉ ነበር:: ለመከራ ዘመን ስንቅ የሚሆነን በሰላሙ
ዘመን የተያዘ ስንቅ ነውና::
+በዚያው አንጻር ደግሞ ሠርቶ መብላት ይገባልና ሥራ
ሲፈልጉ መክስምያኖስ ሠራዊት መሰብሰብ ጀመረ::
እነርሱም ከሠራዊቱ ዘንድ ተቆጥረው የምድራዊ ንጉሥ
ጭፍሮች ሆኑ:: በእርግጥ በዘመናችን ለክርስትና
አይመቹም ከሚባልላቸው ሥራዎች አንዱ ውትድርና
ነው::
ሲፈልጉ መክስምያኖስ ሠራዊት መሰብሰብ ጀመረ::
እነርሱም ከሠራዊቱ ዘንድ ተቆጥረው የምድራዊ ንጉሥ
ጭፍሮች ሆኑ:: በእርግጥ በዘመናችን ለክርስትና
አይመቹም ከሚባልላቸው ሥራዎች አንዱ ውትድርና
ነው::
+ነገር ግን ብዙ ቅዱሳንን ስትመለከቷቸው ሙያቸው
ይሔው ነበር:: ቅዱሳን ባኮስና ሰርጊስ ጊዜው የሰላምም
ይሁን የጦርነት ይጾማሉ: ይጸልያሉ: ይመጸውታሉ::
እንዲህ እንዲህ እያሉም ዘመናት አለፉ::
ይሔው ነበር:: ቅዱሳን ባኮስና ሰርጊስ ጊዜው የሰላምም
ይሁን የጦርነት ይጾማሉ: ይጸልያሉ: ይመጸውታሉ::
እንዲህ እንዲህ እያሉም ዘመናት አለፉ::
+ከቆይታ በሁዋላ ግን ሰይጣን ያደረበት ንጉሡ
መክስምያኖስ ጣዖት አመለከ:: አዋጅም አውጥቶ
ክርስቲያኖችን ያሰቃይ: ይገድልም ያዘ:: ቅዱሳኑ ይህንን
ሲሰሙ አዘኑ::
መክስምያኖስ ጣዖት አመለከ:: አዋጅም አውጥቶ
ክርስቲያኖችን ያሰቃይ: ይገድልም ያዘ:: ቅዱሳኑ ይህንን
ሲሰሙ አዘኑ::
+ቁጭ ብለውም ተወያዩ:: በልባቸው ፍቅረ ክርስቶስ
ይነድ ነበርና ወጣትነታቸው: መልካቸው: ተወዳጅነታቸው
ሁሉ ሊያታልላቸው አልቻለም:: እንደ አንድ ልብ መካሪ:
እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ ስለ ሃይማኖት ሊሰው ወሰኑ::
ይነድ ነበርና ወጣትነታቸው: መልካቸው: ተወዳጅነታቸው
ሁሉ ሊያታልላቸው አልቻለም:: እንደ አንድ ልብ መካሪ:
እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ ስለ ሃይማኖት ሊሰው ወሰኑ::
+በማግስቱም ንጉሡ ወደ ሾመው የቅርብ አለቃቸው
ቀረቡና "የምንነግርህ ነገር አለን" አሉት:: "እሺ"
ሲላቸው በወገባቸው ያለውን የክብር መታጠቀያና የክብር
ልብሳቸውን በፊቱ ወረወሩለትና "እኛ የክርስቶስ ጭፍሮች
ነንና ከዚህ በሁዋላ ላንተ: ለጣዖት አምላኪው
አንታዘዝም" አሉት::
ቀረቡና "የምንነግርህ ነገር አለን" አሉት:: "እሺ"
ሲላቸው በወገባቸው ያለውን የክብር መታጠቀያና የክብር
ልብሳቸውን በፊቱ ወረወሩለትና "እኛ የክርስቶስ ጭፍሮች
ነንና ከዚህ በሁዋላ ላንተ: ለጣዖት አምላኪው
አንታዘዝም" አሉት::
+መኮንኑ ነዶታልና አስገረፋቸው: አሳሰራቸው:: በረሃብና
በጥም: በብዙ መክፈልተ ኩነኔም አሰቃያቸው:: እነርሱ
ግን ጽኑዓን ነበሩና አልቻሏቸውም:: ጥቅምት 4 ቀን በሆነ
ጊዜ ግን 2ቱን ለያዩዋቸው::
በጥም: በብዙ መክፈልተ ኩነኔም አሰቃያቸው:: እነርሱ
ግን ጽኑዓን ነበሩና አልቻሏቸውም:: ጥቅምት 4 ቀን በሆነ
ጊዜ ግን 2ቱን ለያዩዋቸው::
ቅዱስ ባኮስን ለብቻው ወስደው ትልቅ ድንጋይ በአንገቱ
ላይ አሠሩበትና ባሕር ውስጥ አሰጠሙት::
ላይ አሠሩበትና ባሕር ውስጥ አሰጠሙት::
+ነፍሱም ከስጋው ስትለይ ባሕር ወደ ዳር
አስወጣችው:: በአካባባቢውም "ባባ" እና "ማማ"
የሚባሉ ባሕታውያን ነበሩና እግዚአብሔር እንዲገንዙት
አዘዛቸው:: ሲሔዱም ቅዱስ ሥጋውን አንበሳና ተኩላ
ሲጠብቁት አግኝተው: በታላቅ ዝማሬ ገንዘው: በራሳቸው
ተሸክመው ወስደው: በበዓታቸው ውስጥ ቀበሩት::
አስወጣችው:: በአካባባቢውም "ባባ" እና "ማማ"
የሚባሉ ባሕታውያን ነበሩና እግዚአብሔር እንዲገንዙት
አዘዛቸው:: ሲሔዱም ቅዱስ ሥጋውን አንበሳና ተኩላ
ሲጠብቁት አግኝተው: በታላቅ ዝማሬ ገንዘው: በራሳቸው
ተሸክመው ወስደው: በበዓታቸው ውስጥ ቀበሩት::
+ቅዱስ ሰርጊስን ደግሞ ለ6 ቀናት ካሠሩት በሁዋላ
በዚህች ቀን እጁንና እግሩን በእንጨት ላይ ቸንክረው:
በእንስሳት ጭራ ላይ አስረው ሲጐትቱት ውለዋል::
አንገቱን በሰየፉት ጊዜም አንዲት ወጣት ደሙን ተቀብላ
በረከትን አግኝታለች:: የመከራ ዘመን ካለፈ በሁዋላም
ለቅዱሳኑ ቤተ ክርስቲያን ታንጾ በዚህች ቀን ተቀድሷል::
ተአምራትም ታይተዋል::
በዚህች ቀን እጁንና እግሩን በእንጨት ላይ ቸንክረው:
በእንስሳት ጭራ ላይ አስረው ሲጐትቱት ውለዋል::
አንገቱን በሰየፉት ጊዜም አንዲት ወጣት ደሙን ተቀብላ
በረከትን አግኝታለች:: የመከራ ዘመን ካለፈ በሁዋላም
ለቅዱሳኑ ቤተ ክርስቲያን ታንጾ በዚህች ቀን ተቀድሷል::
ተአምራትም ታይተዋል::
=>አምላከ ሰማዕታት ጽንዓት: ትእግስታቸውን አሳድሮ
ከበረከታቸው ይክፈለን::
ከበረከታቸው ይክፈለን::
=>ጥቅምት 10 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን
በዓላት=
1.ቅዱሳን ባኮስና ሰርጊስ (ሰማዕታት)
2.ቅዱስ ዮሐንስ መስተጋድል
3.አባ አውማንዮስ ሊቀ ዻዻሳት
በዓላት=
1.ቅዱሳን ባኮስና ሰርጊስ (ሰማዕታት)
2.ቅዱስ ዮሐንስ መስተጋድል
3.አባ አውማንዮስ ሊቀ ዻዻሳት
=>ወርሐዊ በዓላት
1.ቅዱስ ናትናኤል ሐዋርያ
2.ቅዱስ ኒቆላዎስ ዘሃገረ ሜራ
3.አቡነ መልክዐ ክርስቶስ
4.ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ (ወልደ እልፍዮስ)
5.ቅድስት ዕሌኒ ንግስት
6.ታላቁ ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ
7.ቅዱስ እፀ መስቀል
1.ቅዱስ ናትናኤል ሐዋርያ
2.ቅዱስ ኒቆላዎስ ዘሃገረ ሜራ
3.አቡነ መልክዐ ክርስቶስ
4.ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ (ወልደ እልፍዮስ)
5.ቅድስት ዕሌኒ ንግስት
6.ታላቁ ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ
7.ቅዱስ እፀ መስቀል
=>+"+ ከክርስቶስ ፍቅር ማን ይለየናል? መከራ: ወይስ
ጭንቀት: ወይስ ስደት: ወይስ ራብ: ወይስ ራቁትነት:
ወይስ ፍርሃት: ወይስ ሰይፍ ነውን?
'ስለ አንተ ቀኑን ሁሉ እንገደላለን:: እንደሚታረዱ በጐች
ተቈጠርን'
ተብሎ እንደ ተጻፈ ነው::
በዚህ ሁሉ ግን በወደደን በእርሱ ከአሸናፊዎች
እንበልጣለን:: +"+ (ሮሜ. 8:35-38)
ጭንቀት: ወይስ ስደት: ወይስ ራብ: ወይስ ራቁትነት:
ወይስ ፍርሃት: ወይስ ሰይፍ ነውን?
'ስለ አንተ ቀኑን ሁሉ እንገደላለን:: እንደሚታረዱ በጐች
ተቈጠርን'
ተብሎ እንደ ተጻፈ ነው::
በዚህ ሁሉ ግን በወደደን በእርሱ ከአሸናፊዎች
እንበልጣለን:: +"+ (ሮሜ. 8:35-38)
<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>