ደብረዘይት ምን እየሆነ ነው? - አትሮንስ ዘተዋሕዶ

አትሮንስ ዘተዋሕዶ

በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ሥርዓትና ደንብን የጠበቁ ጽሑፎችና ምስሎች በመ/ር ቀሲስ ንጋቱ አበበ እየተዘጋጀ የሚቀርብበት ድኅረ ገጽ ነው።

Breaking

Post Top Ad

Responsive Ads Here

Saturday, September 28, 2019

ደብረዘይት ምን እየሆነ ነው?




ትናንት በደብረ ዘይት ከተማ የመስቀል በዓልን ለማክበር ሰንበት ተማሪዎች በለበሱት ልብስ ምክንያት
ፖሊስ "መልበስ አትችሉም" በማለቱ በተፈጠረው ችግር ደመራ ሳይለኮስ ቀርቶ ነበር:: ይሁን እንጂ
ማንነታችው የማይታወቁ ጎረምሶች ሌሊት 5:00 አካባቢ ካህናት እና ምእመናን በሌሉበት ደመራውን
ለኩሰው አንድደውት አድረዋል::
የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ የሆኑት ብጹእ አቡነ ጎርጎርዮስ በችግሩ መንስኤ ላይ እና
በተፈጠረው ሥርዓት አልበኝነት ላይ ከክልሉ ባለሥልጣናት ጋር ለመወያየት ዛሬ ቀን ከ 7:00 ጀምሮ
ከከንቲባ ጽህፈት ቤት እንደገቡ ሳይወጡ በመዋላቸው "አባታችንን ልቀቁልን" ከሚሉ ምእመናን ጋር
ፖሊስ በድጋሚ መጋጨቱን አረጋግጬአለሁ::
ማንነታቸው በውል ያልታወቁ "ቄሮ ነን" የሚሉ ወጣቶች የሊቀጳጳሱን መፈታት ለመጠባበቅ በከንቲባ
ጽህፈት ቤት ከተሰበሰቡ ምእመናን ጋር ምሽት ላይ ግብግብ በመፍጠራቸው የክልሉ ፖሊስ አስልቃሽ
ጭስ በመተኮስ ምእመናንን የበተነ ሲሆን "ቄሮ ነን" ባዮቹን ጽህፈት ቤቱ ግቢ ውስጥ ሰብስቦ
እንደዘጋባችውም ሰምቻለሁ:
ሊቀጳጳሱ ለውይይት ወደ ከንቲባዋ የመስተዳድር ቢሮ ሃያ ከሚሆኑ አገልጋዮች ጋር እንደገቡ እስከምሽቱ
1:00 ምክንያቱ በውል በማይታወቅ ሁኔታ ቆይተው የነበረ ሲሆን አሁን በስልክ እንደሰማሁት ግን
ተለቀው ወደሀገረ ስብከታቸው ገብተዋል::




source በኃይሉ ደምሴ

Post Bottom Ad