ግብረ
ሰዶማውያን ወደ ኢትዮጵያ እንዳይገቡ ቅዱስ ሲኖዶስ አወገዘ፤
በቱሪዝም
ሽፋን ወደ ኢትዮጵያ እንመጣለን የሚሉ የተደራጁ ግብረ ሰዶማውያንን: መሬቷና ሕዝቡ እንዳይቀበሉ ቅዱስ ሲኖዶስ አወገዘ፤ በመግለጫው ያካትተዋል::
• መንግሥትም
እንዲያወግዝና የወንጀል ሕጉን በማጥበቅ ቁርጠኝነቱን እንዲያሳይ ጠየቀ፤
• ቶቶ
ቱርስ፣በቱሪዝም ሽፋን ድርጊቱን ለማስፋፋት እንዳቀደበት ጉባኤው በስፋት ተወያየ፤
• ድርጊቱ፥
በሃይማኖት ኀጢአት፣ በባህል ነውርና አጸያፊ፣ በኢትዮጵያ ሕግ ወንጀል ነው፤
ቅዱስ ሲኖዶስ ያወጣውን መመሪያ በመከተል መንግስትም ግብረ ሰዶማውያን ወደ ቅድስት ሃገራችን ኢተዮጵያ እንዳይገቡ ትልቅ ውሳኔ ሊወስን ይገባል፡፡ ሀገራችን ያለፉትን ረጅም ዘመናት ባህሏን፣ እምነቷን ጠብቃ የሆረች ሀገር ናት፤ ዛሬም በዚህ ትውልድ ሀገራችን የነበራት የቀድሞው የአባቶቻችን ሃይማኖት፣ባህልና ወግ ተጠብቆ ለትውልድ ሊተላለፍ ይገባል፡፡ ቱሪዝምን ሽፋን በማድረግ ግብረ ሰዶማውያንን ለማስፋፋት የሚመጣውን ቡድን በአፅንኦት ልንቃወም ይገባል፡፡ ቅዱስ ሲኖዶስ ያወጣውን መመሪያ እኛ ልጆቿ በመቀበልና በመደገፍ ሀገራችንን እና ሃይማኖታችንን ልንጠብቅ ይገባል፡፡