ስብኩ ወንጌለ ለኩሉ ፍጥረት፤ ማር 16፤15
ይህን ቃል የተናገረው ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። እኛም ይህንን አደራ ስንቀበል በመሃላ ነውና ሕዝበ ክርስቲያኑን በሃይማኖት ጸንተን እናገለግለው ዘንድ በጸሎት ሊያግዘን ይገባል። በቅድስት ሥላሴ ኮሌጅ በነበርኩበት ወቅት ብዙ የሚያሳዝኑና አልፎ አልፎም የሚያስደስቱ ዘርፈ ጉዳዮች አሉና ሌላ ጊዜ በደንብ እመለስበታለሁ። ምክንያቱም ለቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን የሚበጃትን ነገር ከማድረግ ወደ ኋላ አንልም። እኔ ግን የልመናየን ድምጽ ሰምቷልና እግዚአብሔር ይመስገን ደግሞም እንኳን ደስ አላችሁ ውድ ጓደኞቼ እላለሁ።