ካለፈው የቀጠለ...................
ቅርሱ የሚገኝበት የጉዳት ሁኔታ
የሰሜን አቅጣጫ ፊት ለፊቱ ግንብ (ዋናው መግቢያ)
·
በሰሜን ምስራቅ የሚገኘው ጠርዝ ቁልቁል
በረጅም ተነስጥቋል
·
በሰሜን ምስራቅ ጠርዝ የሚገኘው በር
የላይኛው ቀሰተ ደመና ግንብ ፈራርሷል
·
ከዋናው መግቢያ በር በስተግራ የሚገኘው
በር የላይኛው ግንብ ሙሉ ለሙሉ ተሰንጥቋል
·
ከዋናው መግቢያ በር በስተግራ የሚገኘው
ግንብ ከላይ ወደ ታች በግማሽ ተሰንጥቋል
·
የቅድስቱ የላይኛው የፈራረሰው ግድግዳ
ክፍል በጭቃ ግንብ ተስርቷል
የምስራቅ አቅጣጫ ግንብ
·
በሰሜን መእራብ ጠርዝ የሚገኘው በር
የላይኛው ቀስተ ደመና ግንብ ፈራርሷል
·
አራት የተለያዩ ቦታዎች ላይ የተሰነጠቀ
ቁልቁል ወደታች ሶስት ቦታ በመካከለኛ ደረጃ የተሰነጠቀ
·
የቅድስቱ የላይኛው የፈራረሰው ግድግዳ
ክፍል በጭቃ ግንብ ተሰርቷል
የምስራቅ አቅጣጫ ግንብ
·
የሁለቱ በሮች በላይ የሚገኘው ግንብ
ቁልቁል ሁለት ቦታ በመካከለኛ ደረጃ የተሰነጠቀ
·
በድንጋይና ጭቃ ከተገነባው (የተደፈነው)
ግንብ ላይ የሚገኘው የኖራ ግንብ ቁልቁል ሶስት ቦታ በመካከለኛ ደረጃ የተሰነጠቀ
·
የውጪኛው የላይኛው የፈራረሰው ግድግዳ
ክፍል በጭቃ ግንብ ተሰርቷል
የደቡብ አቅጣጫ ግንብ
·
በድንጋይና ጭቃ ከተገነባው (የተደፈነው)
ግንብ ላይ የሚገኘው የኖራ ግንብ ቁልቁል ሶስት ቦታ በመካከለኛ ደረጃ የተሰነጠቀ
·
የሁለቱ በሮች በላይ የሚገኘው ግንብ
ቁልቁል ሁለት ቦታ በመካከለኛ ደረጃ የተሰነጠቀ
በግቢው ውስጥ የሚገኘው ሙዚየም
·
የሙዚየሙ አራና ግድግዳ የሚጋጠሙበት
ቦታ ወደ ውስጥ እያሰረገ ግንቡ እርጥብት ያዘለ መሆኑ
·
የጣራው ሁለት የውሃ ማስወገጃ አሸንዳዎች
በአፈር ዘግቶት ተደፍነው ጣራው ላይ ውሃ እያዘለና በዲንጋዩቹ እየሰረገ የሕንጻውን ግንብ ወለልና የኮርኒሱ ጣውላ እያረጠበ መሆኑ
·
አብዛኛው ውጫዊው ግድግዳ በቁጥቋጦዎቻ
አረሞች ተሸፍኗል
ከዚህ በፊት የተደረጉ የጥገናና ግንባታ ስራዎች
·
አግባብ ያላቸው ቢሮዎችና መምሪያዎች
ሳያውቁ የቅድስቱ ወለል በሲሚንቶ ከውስጥ ከተገረፈ በኋላ ከላይ ጅብስምና ቀለም የተቀባ መሆኑ
·
በምስራቅ አቅጣጫ የቅድስቱ ክፍት በሮች
በመድፈን መስኮት ተስርቷል
·
የቤተክርስቲያኗ ጣራ በቆርቆሮ ተቀይሯል
·
በውጭ በኩል ዙሪያውን የሸክላ ምሶሶ
በአዲስ መልክ ተገንብቷል
·
የቤተ መቅደሱ መግቢያ በግራ በኩል
ለምጽዋት መሰብሰቢያ ግንቡን ስልሳ በስላ ሳ.ሜ ስፋት በመቆፍቆፍ ተገንብቷል
·
ወለሉ ዙሪያውን በሲሚንቶ ተሰርቷል፤
የወለሉ ከፍታም እንዲጨምር ተደርጓል
·
በጣሊያን ወረራ ወቅት የቤተክርስቲያኑን
ካርታና ፕላን በ1931 ተሰርቷል
·
ከ1971 ኢንጂሊኒ በተባለ የዩኔስኮ
መሃንዲስ ማስተር ፕላን ተሰርቷል
·
በ1996 የቤተክርስቲያኑ ዋና ግድግዳ
ጣራውን መሸከም ባለመቻሉ ከውጭ የሸክላ ቢሞችን በመስራት የቆርቆሮ ጣሪያ እንዲሸከመው ተደርጓል
·
የቤተክርስቲያኑ ቤተልሔም በአዲስ ተሰርቷል
·
አዳዲስ የመቃብር ቤት ሕንጻዎች ተገንብተዋል
ይቆየን......................................................