ጨረስኩ ሳልጀምረው - አትሮንስ ዘተዋሕዶ

አትሮንስ ዘተዋሕዶ

በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ሥርዓትና ደንብን የጠበቁ ጽሑፎችና ምስሎች በመ/ር ቀሲስ ንጋቱ አበበ እየተዘጋጀ የሚቀርብበት ድኅረ ገጽ ነው።

Breaking

Post Top Ad

Responsive Ads Here

Thursday, May 28, 2015

ጨረስኩ ሳልጀምረው


ከፊደላት ተራ ከሆሄ ገብቼ
ክብርሽን ለመግለጽ ሞልቼ አስፍቼ
አበው ሲናገሩ ክብርሽን ሰምቼ
ቃላትን በቃላት መርጬ አሳክቼ
“ሀ” ብዬ ጀመርኩ ልናገር ጸጋሽን
መጽሐፍ ከሚለው በልቤ ያለውን
አባቶች ቅዱሳን ያስተላለፉትን
በሕይወት ከእነርሱ የተቀበልኩትን
ከእነ “ሀ” ጎረቤት ከእነ “ለ” አዝማዳት
በሰባት በሰባት ከተከፋፈሉት
ከላይ እስከታች ከተደረደሩት
እስከነ “ፐ” ድረድ ከተሰበሰቡት
ያንንም ሳመጣው ይህንም ስመዘው
ጥንት የመረጥኩትን መልሼ ስተወው
ፊት ያስገባሁትን ኋላ ስመልሰው
አንዱን አስገብቼ ሌላውን ሳወጣው
ፈጽሜአለሁ ብዬ የጻፍኩትን ባየው
ድንግል ውዳሴሽን ጨረስኩ ሳልጀምረው። 

Post Bottom Ad