2ኛ ወደ ጢሞቴዎስ ሰዎች በምዕራፍ 2፤22 ላይ እንዲህ
የሚል መልእክትን እናነባለን፤ ከክፉ የጎልማሳነት ምኞት ግን ሽሽ፤ በንጹህም ልብ ጌታን ከሚጠሩ ጋር ጽድቅን፤ እምነትን፤ ፍቅርን
እና ሰላምን አጥብቀህ ተከተል። ይህን ቃል የተናገረው ቀድሞ ክርስቲያኖችን በማሳደድ እንዲሁም በማስገደል፤ ለኦሪት ሕግ ቀናተኛ
ነኝ በማለት ይናገር የነበረውና በመጨረሻም ክርስቲያኖችን ለመግደል፤ ለመጨፍጨፍ እና ለማሳደድ የፈቃድ ደብዳቤ ይዞ ወደ ደማስቆ
በሚጓዝበት ወቅት ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገልጾለት ወደ ክርስትና አምነት የተመለሰው ብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ
ነው። ክፉ፤ ጎልማሳነት፤ ምኞት የሚሉትን ቃላት ለይተን ብንመለከታቸው በክርስትና ሕይወታችን ላይ ለውጦችን ለማምጣት ግልጽ የሆነ
መልእክት አዘል ወይም ተሎ የመገንዘብ ሁኔታ ሊፈጠር ይችላል። ለምሳሌ ከታላቁ አባት ቅዱስ መቃሬዎስ ገድል ስንመለከት እንዲህ የሚል
ታሪክ እናገኛለን። ትምህርቱም ስለ ትህትና እንጂ ክፉ ነገር ወይም
ምኞት
አይደለም። አባ ወቅሪስ ድንዲህ አለ፦ አባ መቃርዮስን ልጎበኘው ሄድኩና በሕይወት ለመኖት የሚጠቅመኝን አንድ ቃል ንገረኝ አልኩት፡ እርሱም ብነግርህ ሰምተኸኝ ታደርገዋለህ? አለኝ። እኔም አምነቴና ፍቅሬ ካንተ የተሰወሩ አይደሉም አልኩት። አባ መቃርዮስም እንዲህ አለኝ። በ እውነት እኔ የምግባር ሕይወት ይጎድለኛል። አንተ ግን ጥሩ ነህ ነገር ግን የዚህ ዓለም ትምህርት የሚያመጣውን ክብርና ዝና አውልቀህ ብትጥልና የቀራጩን ትህትና ብትላበስ በሕይወት ትኖራለህ። እነዚህን ነገሮች በተነገረኝ ጊዜ ሃሳቦቸ ሁሉ በንነው ጠፉ። ይቅርታውን በጠየኩትም ጊዜ በላዬ ላይ ከጸለየልኝ በኋላ አሰናበተኝ። የውስጤ ሃሳቦች ሁሉ ከ እግዚአብሔር ሰው ከአባ መቃርዮስ የተሰወሩ እንዳልሆኑ ተረዳሁ። ወደ እርሱ በሄድኩ ጊዜም ሁሉ እንዳዳምጠው ከሚያደርገኝ ከጸጋው የተነሳ እርዳለሁ ለ እኔም ትህትናን የምለማመድበት አጋጣሚ ነበር። በማለት ስለ ትህትና እና ፍቅር ገድላቸው ያስተምረናል። ቅዱስ ጳውሎስ ከክፉ የጎልማሳነት ምኞት ግን ሽሽ ማለቱ ትህትናን እና ፍቅርን አዘውትረን እንድንከተል ጽፎልናል።
አይደለም። አባ ወቅሪስ ድንዲህ አለ፦ አባ መቃርዮስን ልጎበኘው ሄድኩና በሕይወት ለመኖት የሚጠቅመኝን አንድ ቃል ንገረኝ አልኩት፡ እርሱም ብነግርህ ሰምተኸኝ ታደርገዋለህ? አለኝ። እኔም አምነቴና ፍቅሬ ካንተ የተሰወሩ አይደሉም አልኩት። አባ መቃርዮስም እንዲህ አለኝ። በ እውነት እኔ የምግባር ሕይወት ይጎድለኛል። አንተ ግን ጥሩ ነህ ነገር ግን የዚህ ዓለም ትምህርት የሚያመጣውን ክብርና ዝና አውልቀህ ብትጥልና የቀራጩን ትህትና ብትላበስ በሕይወት ትኖራለህ። እነዚህን ነገሮች በተነገረኝ ጊዜ ሃሳቦቸ ሁሉ በንነው ጠፉ። ይቅርታውን በጠየኩትም ጊዜ በላዬ ላይ ከጸለየልኝ በኋላ አሰናበተኝ። የውስጤ ሃሳቦች ሁሉ ከ እግዚአብሔር ሰው ከአባ መቃርዮስ የተሰወሩ እንዳልሆኑ ተረዳሁ። ወደ እርሱ በሄድኩ ጊዜም ሁሉ እንዳዳምጠው ከሚያደርገኝ ከጸጋው የተነሳ እርዳለሁ ለ እኔም ትህትናን የምለማመድበት አጋጣሚ ነበር። በማለት ስለ ትህትና እና ፍቅር ገድላቸው ያስተምረናል። ቅዱስ ጳውሎስ ከክፉ የጎልማሳነት ምኞት ግን ሽሽ ማለቱ ትህትናን እና ፍቅርን አዘውትረን እንድንከተል ጽፎልናል።
ጎልማሳነት፦ የጎልማሳነት እድሜ ከሃያዎቹ እስከ አርባዎቹ የሚደርስ የእድሜ ዘመን ነው። በዚህ እድሜ ውስጥ ብዙ የእሳትነት ባህርይ የሚንጸባረቅባቸው በመሆኑ፤ የምንሰራቸው ስራዎች በአጠቃላይ በአስተሳሰብ፤ በማህበራዊ ኑሮ፤ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ የችኩልነት ባሕርይ የሚታይበት በመሆኑ፤ አብዛኛውን ጊዜ ለሃጢአት ስራዎች እንጋለጣለን። ለዚህ ሃጢአት ስራ እንዳንጋለጥ ቅዱስ ጳውሎስ የጻፈልንን መልእክት ማንበብ እና መረዳት ይገባል።
ምኞት፦ የሚገባ እና የማይገባ ምኞት አለ። የሰው ልጅ በማይገባ ምኞት ከተጠለፈ የሰይጣን ፈተና ይበዛበታል። አወዳደቁም በስጋም በነፍሱም ይከፋል። መጨረሻውም አያምርም ምክንያቱም የማይረባ ምኞቱን ለመፈጸም በሚጥርበት ወቅት በኃጢአት እየተዘፈቀ መሆኑን መረዳት አለበት። በመጽሐፍ እንዲህ የሚል መልእክት ተጽፏል ኃጢአትም ከአደገች በኋላ ሞትን ትወልዳለች። ያዕ 1፤5
ክፍ ነገር፦ የመልካም ነገር ተቃራኒው ክፉ ነገር ነው። በግብር፤ በአንደበት፤ በሃሳብ በተለያዩ የክፉ ስራ ድርጊት የሚፈጸም ሁሉ በሰውም፤ በእግዚአብሔርም የማይወደድ፤ የተጠላ፤ የሚያሳዝን ነገር ሁሉ ክፉ ነገር ይባላል።