በቅድሚያ ልናውቅ የሚገባን ነገር አለ። እሱም ሃይማኖታችንን ጠንቅቀን ማወቅ እና ቅዱሳን አባቶቻችን የሄዱበትን የሃይማኖት መንገድ መከተል ነው። ለምሳሌ፤

የሕይወትና የክብር ባለቤት ወደ ሆነው የባህርይ አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ ያደረጉትን ጉዞ የሚያሳይ ስለሆነ በዚህ ብሎግ ላይ የምናስተላልፋቸው መልእክቶች የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ዶግማ፤ ቀኖና እና ትውፊትን የጠበቀ ከመሆኑም በላይ ከአባቶቻችን የወረስናቸውን ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን የጠበቀ ትምህርት፤ መዝሙሮች፤ ስብከቶች፤ እና ሌሎች ጥሩ ምክር አዘል ቁም ነገሮችን አትሮንስ ታስተላልፋለች::
2) ሰው የፈጣሪውን ሕግ በማፍረሱ ምክንያት ወደዚህ ዓለም ቀጥሎ ወደ አምላኩ የሚያደርሰውን እውነተኛ መንገድ አጥቶ አምስት ሽህ አምስት መቶ ዘመን ሲባዝን ኖረ:: ይህ ዓመተ ፍዳ ሲያልቅ እግዚአብሔር ወልድ በተለየ አካሉ ከቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍስዋ ነፍስ ነስቶ አንድ አካል አንድ ባሕርይ ሆኖ ወደዚህ ዓለም መጥቶ ሰውን ከፈጣሪው ጋር የሚያገናኘውን እውነተኛውን መንገድ አስተማረ:: ገላ 4;4:: እርሱም "አነ ውእቱ ፍኖተ ጽድቅ ወሕይወት - የጽድቅና የሕይወት መንገድ እኔ ነኝ" በማለት ከፈጣሪው አንድነት ተለይቶ ከክብር ተራቁቶ የነበረውን የሰው ልጅ ወደራሱ አንድነት ሊያዋህደው እንደመጣ አስረዳ:: እርሱን በፍጽም ሕይወታቸው ለሚመስሉት ወደ ሕይወትና ክብር የምትወስደውን ጠባብ መንገድ በቃል ያስተማረና በተግባር ሠርቶ ሥሩ ያለ ቅዱሳንን የጠራ የተቀበለና ያከበረ እውነተኛው ፍኖተ ቅዱሳን ኢየሱስ ክርስቶስ ለወዳጆቹ ያለውን ፍቅርና ተቆርቋነት እንዲሁም ያዘጋጀላቸውን ክብር ስለሚያስረዳ የአትሮንስ ብሎግ ጉዟችን ቅዱሳን አባቶቻችን የተከተሉትን መንገድ መከተል ነው።
3) ነቢየ እግዚአብሔር ሆሴዕ "ይህን ነገር የሚያስተውል ጠቢብ የሚያውቃትም አስተዋይ ማነው? የእግዚአብሔር መንገድ ቅን ነው ጻድቃንም ይሄዱበታል ተላላፊዎች ግን ይወድቁበታ" ብሎ የጻድቃንን እና የኃጥአንን መንገድ ልዩነት አስረድቷል:: ሆሴ 14:9 ጠቢቡ ሰሎሞን" የጻድቃን መንገድ እንደ ንጋት ብርሃን ነው ሙሉ ቀን እስኪሆንም ድረስ እየተጨመረ ይበራል" ይላል ምሳ 4:18
ስለዚህ አትሮንስ ብሎግ ጻድቃን የሄዱበትን ቅንና ርቱዕ የሆነውን፤ እግዚአብሔር ቅድስናን እና ፍጹምነትን ለሚሹ ያዘጋጀውን መንገድ ስለሚያሳይ፤ አትሮንስ ብሎግ የምታስተላልፋቸውን ቁም ነገሮች በየጊዜው እንድትከታተሉ ስትል ጥሪዋን ታስተላልፋለች።
ስለዚህ አትሮንስ ብሎግ ጻድቃን የሄዱበትን ቅንና ርቱዕ የሆነውን፤ እግዚአብሔር ቅድስናን እና ፍጹምነትን ለሚሹ ያዘጋጀውን መንገድ ስለሚያሳይ፤ አትሮንስ ብሎግ የምታስተላልፋቸውን ቁም ነገሮች በየጊዜው እንድትከታተሉ ስትል ጥሪዋን ታስተላልፋለች።
የቅዱሳን በረከታቸው እና ረድኤታቸው አይለየን::